ሰበር መረጃ!

ሰበር ዜና

የአ/አ ምክትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ ከቦታቸው ሊነሱ እንደሆነ በአንዳንድ ሰዎች ዛሬ ሲገለፅ ነበር። ይህ መረጃ ትክክል እንደሆነ እና ም/ከንቲባው ከሳምንት በላይ ስልጣናቸው ላይ እንደማይቆዩ ታማኝ ምንጮች ማምሻውን አሳውቀውኛል።

ምንጭ 1: “ም/ከንቲባው ስራቸውን ለመቀጠል ፍላጎት ነበራቸው። ነገር ግን ስራቸው ላይ እንደማይቆዩ ላረጋግጥልህ እችላለሁ፣ ምናልባት ከዚህ በሁዋላ አንድ ሳምንት ቢቆዩ ነው። ለምን ሊነሱ እንደተፈለገ ግን ግልፅ አይደለም፣ ምናልባት የፓርቲያቸው ውሳኔ ሊሆን ይችላል።”

ምንጭ 2: “መረጃው ትክክል ነው። አሁን ባለው ጭምጭምታ የገቢዎች ሚኒስትር ሀላፊዋ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ኢ/ር ታከለን ይተካሉ ተብሎ ተገምቷል።”

በዚህ ላይ ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰኝ አቀርባለሁ!

@eliasmeseret @EliasAds

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *